ተቃውሞ በሊባኖስ የወያኔ ቆንስላ ላይ
በሊባኖስ ቤይሩት ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ፣ ህይወቷን አጠፋች የተባለችው የዓለም ደቻሳ ሞት ከተነገረበት ማግስት አንስቶ ቤይሩት ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ በመሄድ ቁጣቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን የጂዳው ወኪላችን ነበዩ ሲራክ ዘግቧል ። ሊባኖስ ቤይሩት ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ፣ ህይወቷን አጠፋች የተባለችው የዓለም ደቻሳ ሞት ከተነገረበት ማግስት አንስቶ ቤይሩት ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ በመሄድ ቁጣቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን የጂዳው ወኪላችን ነበዩ ሲራክ ዘግቧል ። ዓለም ቆንስላው በር ላይ ስተሰቃይ በነበረበት ወቅት የሚደርስላት ማጣቷ ያስቆጫቸው እነዚሁ ኢትዮጵያውያን የቆንስላው ባለሥልጣናት መብታችንን ያስጠብቁ አለያም ለቀው ይውጡ በማለት በተለያዩ መንገዶች ተቃወሞአቸውን እየገለጹ ነው ። በቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጀነራል በበኩላቸው ዜጎች ህጋዊ ከለላ እንዲያገኙ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና ጉዳዩንም የሊባኖስ መንግሥት እየተመለከተው መሆኑን ለዶቼቬለ አስታውቀዋል።
[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/A52CCB42_2_dwdownload.mp3[/podcast]