በጂዳ የኢትዮጵያውያን ክርስቲያን እስረኞችና የወያኔ ቆንስላ

ወደ 3 ወር ለሚጠጋ ጊዜ ጅዳ ሳውዲ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙት 36 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በታሠሩበት ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች ለደረሰብን በደል ፍትህ እንድናገኝ አላደረጉም ሲሉ ያቀረቡትን ወቀሳ በጂዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ አስተባበለ። በጂዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ኑረዲን ሙስጠፋ ቆንስላው ባለስልጣናት ታሳሪዎቹን ያሉበት ድረስ ሄደው እንዳነጋገሩዋቸውና ኢትዮጵያውያኑ በእስር ቤት ተፈፀመብን የሚሉት በደል እንዲጣራ ለእስር ቤቱ ሃላፊዎች መንገራቸውን አስታውቀዋል። ያነጋገራቸው ነብዩ ሲራክ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/EE63CE76_2_dwdownload.mp3[/podcast]