በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሁኔታ
በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች ለወራት ሲማጸኑ ከነበሩበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጽ/ቤት ደጃፍ በኃይል ወደተለያዩ አካባቢዎች መጋዛቸውን የስደተኞቹ ተወካዮች አስታወቁ።
የኃይል እርምጃውን ማምለጣቸውን የተናገሩ ስደተኞች እንዳመለከቱት፥ የየመን ፖሊስ ኃይል ነው፥ በስደተኞች ጽ/ቤት ተመዝግበው ለበርካታ ዓመታት በዚያች አገር የኖሩትን ጨምሮ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩትን እነኚህን ስደተኞች በከፍተኛ የኅዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እያሳፈረ በብዙ መቶ ኪሎሜትሮች ወደ ራቁ አካባቢዎች ያጓጓዘው።
[podcast]http://media.voanews.com/audio/Ethiopian Refugee in Yemen 04-02-12.Mp3[/podcast]