በኢትዮጵያ የገደማት ይዞታ ያስከተለው ሥጋት

በአሰቦትና በዝቋላ ገዳማት አካባቢ በቅርቡ ቃጠሎ ተነስቶ የነበረበት ሁኔታ፣ በአሰቦት ገዳም ይማር የነበረ አንድ ልጅ፣ መገደሉ፣ እንዲሁም፤ የበርሊኑ ዘጋቢአችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል እንደዘገበው፤ በልማት ስም ፣ የዋልዳባ ገደም መደፈር፣ በዚህ በጀርመን አገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልጋዮችን እና አባቶችን፤ ጉዳዩ አሳስቦአቸዋል። «የገዳሙ አባቶች አለምክንያት ድምጻቸውን አላሰሙም! » ያሉት፣ በጀርመን የሚገኙት መንፈሳዊ አገልጋዮች፣ ለህዝበ ክርስቲያኑ፤ በየአጋጣሚውና በዕለተ እሁድ ሥጋታችንን መግለጽ ይኖርብናል። ለገዳሞቻችንም የተለየ የጸሎት መርኀ-ግብር እንዲወጣ እናድርግ» ሲሉ አሳስበዋል። ያዳምጡ