የዋልድባ ፕሮጀክትና የዋሽንግተን ሰልፍ

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ በሚገኙ ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ከትናንት በስተያ በዋልድባ ገዳም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ነዉ ያሉት ፕሮጀክት እንዲቆም ጠየቁ። ኢትዮጵያዉያኑ ዋሽንግተን በሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ ባደረጉት ሰልፍ ነዉ ጥያቄያቸዉን ያቀረቡት። ኤምባሲዉ በበኩሉ በፅሁፍ በሰጠዉ ምላሽ ፕሮጀክቱ እና ገዳሙ ጭራሽ አይገናኙም፤ ተቃዉሞዉ ሃይማኖታዊ ሳይሆን ፖለቲካዊ አጀንዳ የያዘ ነዉ ማለቱን የዋሽንግተን ዲሲዉ ወኪላችን አበበ ፈለቀ በላከዉ ዘገባ አመልክቷል።

[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/17F86A4C_1_dwdownload.mp3[/podcast]