የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የጡረታ አበል ወደ 1317 ብር ከ36 ሣንቲም ከፍ አለ

አቶ አየለ ጫሚሶ በጠና ታመዋል

ከ1997 አወዛጋቢ ምርጫ በኃላ የአዲሱ ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ አየለ  ጫሚሶ የአልጋ ቁራኛ ሆነዋል፡፡ ሳምንታዊው ሰንደቅ ጋዜጣ በረቡእ እትሙ እንደዘገበው ሊቀመንበሩ በቤተዛታ ሆስፒታል ሲረዱ ቆይተው አሁን ከፍተኛ የውጭ ህክምና እንደሚያሻቸው ተነግሯቸው ከሆስፒታሉ ወጥተዋል፡፡

ህመሙ የጀመራቸው ካለፈው ታህሳስ ወር ወዲህ እንደሆነ የዘገበው ጋዜጣው ሊቀመንበሩ ከፓርቲው ስራ ገለል ካሉ ሰነባብተዋል፡፡ በደም ግፊት፣ በጨጓራ ህመም እንዲሁም  የምግብ መፈጨት ችግርና በአንጀታቸው ላይ የደም መድማት ሁኔታ እንዳጋጠማቸው ዘገባው አብራርቷል፡፡

የአምስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ አየለ ጨሚሶ ታይላንድ ሄደው ለመታከም ህዝብ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው እየተማፀኑ ይገኛሉ፡፡

*                       *                              *

የዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የጡረታ አበል ወደ 1317 ብር 36 ሣንቲም ከፍ አለ

ኢፌድሪ የቀድሞ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የጡረታ አበላቸው ከ1197 ብር ከ60 ሣንቲም ወደ 1317 ብር ከ36 ሣንቲም አለ። በቅርቡ በኑሮ ውድነቱ የተነሳ የተሻሻለው የጡረታ አበል ክፍያ በዝቅተኛ ደረጃ ላሉት ጡረተኞች እስከ 84 በመቶ የሚደርስ ሲሆን ከአንድ ሺህ ብር በላይ የጡረታ አበል ለሚያገኙ ጡረተኞች ግን የ10 በመቶ ጭማሪ ብቻ ነው።

በዚህ መሠረት የቀድሞ የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የ10 በመቶ የጡረታ አበል ጭማሪ 119 ብር ከ76 ሣንቲም ብቻ ነው። ዶ/ር ነጋሶ በቅርቡ የተከበረላቸውን የጡረታ አበላቸውን ከጥቅምት 17 ቀን 2003 ዓ.ም ጀምሮ በየወሩ ወደ ክፍለ ከተማቸው በሚገኘው ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ በማምራት ጀምረዋል።

የጡረታ አበል ከተስተካከለ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሻሻለውን የጡረታ አበላቸውን ዕረቡ የካቲት 2 ቀን 2003 ዓ.ም የተቀበሉ ቢኾንም  በቀድሞ ፕሬዝዳንትታቸው ሊያገኙት የሚገባቸው ሕጋዊ ጥቅማ ጥቅሞች በ1997 ዓ.ም ምርጫ በትውልድ ቦታቸው ደምቢዶሎ በግል ተወዳድረው በማሸነፍ ፓርላማ ከገቡ በኋላ እንደተቋረጠባቸው  ይገኛል፡፡