ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ (1927 – 2003 ዓ.ም) ሲታወሱ


  • ‹‹የምናሠለጥናቸው በሌላ ቋንቋ ተናግረው የሌለ ሃይማኖት እንዲያመጡ አይደለም፡፡›› (ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ በ1991 ዓ.ም ከተናገሩት)
  •  ሥርዓተ ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል፤
(ደጀ ሰላም፤ ማርች 4/2011)፦ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ ማረፋቸውን ትናንት መዘገባችን ይታወሳል። ብፁዕነታቸው በድንገተኛ ሕመም ማረፋቸው የተሰማው ሐሙስ የካቲት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ዘጠኝ ሰዓት ገደማ በመንበረ ፓትርያርኩ ከሚገኘው ማረፊያ ቤታቸው ነው፡፡
ከአንድ ወር በኋላ ሥልጣኑን የሚረከበው የቀጣዩ ቋሚ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ የካቲት 21 ቀን 2003 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፈትኖ ላቀረባቸው በርካታ ዲያቆናት ከሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ጋራ የቅስና ማዕርግ ሰጥተዋል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)