የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አንድ ተማሪውን ከትምህርት አገደ


(ደጀ ሰላም፤ ዲሴምበር 4/2010 ኅዳር 25/2003 .) የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር ጉባኤ ለአዲስ ተመዝጋቢ ደቀ መዛሙርት ባስቀመጠው መስፈርት መሠረት ‹‹ከተቋሙ የቅበላ መስፈርቶች አንዱ የሆነውን በሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወይም በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የተፈረመበት የድጋፍ ደብዳቤ በተሰጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ አላቀረበም፤ በድጋፍ ደብዳቤ ስም ያቀረበውም ማስረጃ ተቀባይነት የሌለው ነው፤ ከአንድ ወር በላይ በትምህርት ገበታው ላይ አልተገኘም››፣  ከሬጅስትራሩ፣ ከአካዳሚክ ዲኑ እና ከበላይ ሐላፊው ዕውቅና ውጭ ወደ ኮሌጁ በሕገ ወጥ መንገድ በመግባት ትምህርት ጀምሯል ያለውን አሰግድ ሣህለ የተባለ ተማሪ አገደ፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)