ሃያ የክህደት፣ የውርደት፣ የዘረኛነትና የዘራፊነት አመታት
ወያኔ የሚያከብረውን 20ኛ የድል አመት አስመልክቶ ከግንቦት 7 የተሰጠ መግለጫ
ሃያ የክህደት፣ የውርደት፣ የዘረኛነትና የዘራፊነት አመታት
ግንቦት 18 2003 ዓ.ም
በደርግና በመንግስቱ ሃይለማሪያም ቦታ ወያኔና መለስ ዜናዊ ከተተኩ 20 አመት ሆነው። ሰሞኑን መለስ ዜናዊ ሃያኛውን የንግስና በአል ለማክበር ከፍተኛ በጀት መድቦ እየተራወጠ ነው። የፈረደበት ህዝብም በአሉን እንዲያጅብ በየቀበሌውና በየመስመሪያ ቤቱ ቀጭን ትእዛዝ ደርሶታል። ያው መንግስቱና ኢሰፓ ሲያደርጉ እንደነበረው ማለት ነው። ዛሬም እንደ ትናንቱ ህዝብ የሃገሩንና የራሱን አራጆቹ ድግስ እንዲያሞቅና ለዲስኩራቸው እንዲያጨበጨብ እየተደረገ ያለው ሠራተኛው በደሞዙ፤ ሌላው ከቀበሌ በሚያገኘው ስኳር፣ ዘይትና ሌሎችም አግልግሎት በኩል በሚመጣበት ማስፈራሪያ ነው። ክቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃገሪቱ ህዝብ በማንኛውም የህይወት ዘርፍ ያለመለስ ዜናዊ ካድሬዎቹ ሳንባ መተንፈስ እንዳይችል የሚያደረገው ሸምቀቆ እየጠበቀ ሄዷል። ብቸኛው ቀጣሪ፤ ስኳርና ዘይት አከፋፋይ፤ የእድገትና የከፍተኛ ትምርት እድል ደልዳይ፤ ፍትህንና የባንክ ብድርን ፈቃጅ ወያኔ ብቻ በሆነበት ሃገር ህዝብ ምርጫው ሰልፍ መውጣት፤ ለወያኔ ገንዘብ ማዋጣት፤ ወያኔ የሚያዘውን ሌላም ትእዛዘ መፈጸም ሆኗል። ይህ ግን እውነታውን አይደብቀውም። ከወያኔ የሻምፓኝ፣ የሽቶ፣ የከበሮ፣ የእልልታና የፉከራ ድግስ ጀርባ ያለው የስርአቱ አስከፊ ገጽታና ክርፋት መሸፋፈኛዎቹን ሰብሮ በአይን መታየቱ በአፍንጫ መሸተቱ አልቀረም።
ያለፉት ሃያ አመታት ለኢትዮጵያ እንደምን ያሉ አመታት ነበሩ?
- ሃያ የወያኔ አመታት ለመጀመሪያ ግዜ በሃገራችን ታሪክ ከአንድ ዘር ብቻ የተሰባሰቡ ጥቂት ግለሰቦች የሃገሪቱን ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ስልጣን፤ የሃገሪቱን ሃብት፣ መሬቱንና ማዕድኑ፤ የሃገር ውስጥና የወጭ ሃገር ንግዱን፤ የኮንስትራክሽን፣ የባንክ፣ የኢንሹራንስ፣ የትራንስፖርት፣ የማምረቻና ማከፋፈያ ስራውን የተቆጣጠሩበት፤ እፍረትና ይሉኝት የለሸ ነውረኛና አደገኛ ስራ የተሰራባቸው አመታት ናቸው።
- ያለፉት 20 አመታት ሃገሪቱ በጥቂት ለዘረፋ ስልጣን በያዙ ዘረኞችና አፋኞች እጅ በመወደቋ ታላቅ የተፈጥሮና የሰው ሃብቷንና እንዲሁም ባለፈው 20 አመታት የተገኘው አንጻራዊ ስላም ተጠቅም ድህነትን ረሃብን ስደትን ሀገራዊ ውርደትን ማስቆም የምትችልበትን እጅግ ታላቅ እድል ያባከነችባቸው አመታት ናቸው።
- ያለፉት 20 አመታት፣ በየትኛዎቹም ኢትዮጵያ መንግስታዊ ስርአቶች ከቶ ተደርገው የማይታወቁ፤ በሃገራችንና በህዝቧ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ሃገራዊ ክህደቶች የተፈጸሙባቸው አመታት ናቸው። ኢትዮጵያችን ከዚህች ሃገር ውስጥ በወጡ ልጆቿ ሳይሆን ለሃገሪቱና ለህዝቧ ከፍተኛ ጥላቻ ባላቸው፤ ሃገሪቱንና ህዝቧን መበቀል የግድ የሆነባቸው፤ ቂም አዝለው ስልጣን በያዙ የውጭ ወራሪዎች እጅ የወደቀች እስክትመስል ሃገራዊና ህዝባዊ ክብሯ አጥታ የተዋረደችባቸው አመታት ናቸው።
- ያለፉት 20 አመታት በየትኛውም ዘመን ስልጣን ላይ የወጡ ገዥዎች አስበውትና አድርገውት በማያውቁት ደረጃ የሃገር ሃብትና ቅርስ ስልጣን ላይ ባሉ ጥቂት የትግራይ ገዥ ጉጅሌ አባላት እየተዘረፈ በባእድ ሃገራት የተከማቸበት አመታት ናቸው። እኝህ አመታት የዘረኛው ገዥ ጉጅሌ አባላት ለዘረፋ እንዲያመቻቸው ያስጠጓቸው የውጭ ሃገራት ዜጎች በሃገራችን ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የህዝቡን ለም መሬት፣ ወርቅ ሌላም ማእድን እንዳሻቸው እየዘረፉና የሃገሪቱን ህዝብ ከባርነት ስርአት ባለተናነሰ የጌታና የሎሌ ግንኙነት እንዳሻቸው እያዋረዱ እንዲያሰሩ ስድ የተለቀቁባቸው አመታት ናቸው።
- ያለፉት 20 አመታት ዳኝነትና ፍትህ የሚባል ነገር ጭራሽኑ ካገር የጠፋበት፤ ዜጎችና ህዝቦች ተቆጪ በሌላቸው በዘርና በጥቅም በተሳሰሩ የገዢው ጉጅሌ የጦር አዛዦች፣ የደህንነት አባላትና ካድሬዎች እንዳሻቸው የሚረሸኑበት፤ ህዝብ ለሰቆቃና ለእስራት የተዳረገበት፤ ሰው በገዛ ቤቱ ውስጥ ሳይቀር የሚሰማውን መናገር እንዳይችል የስጋትና የፍርሃት ቀንበር ውስጥ የወደቀችባቸው፤ እንዲሁም በዘር ማጥፋትና በሰው ልጆች ላይ እንደተፈጸሙ ተደርገው የሚታዩና በአለምአቀፋዊ ወንጀለኛነት የሚያስጠይቁ ታላላቅ ወንጀሎች በመላው ሃገሪቱ ህዝብ ላይ የተፈጸሙባቸው አመታት ናቸው።
በጥቅሉ ያለፉት 20 የወያኔ የግዛት አመታት የኢትዮጵያን ውርደት፤ የህዝቧን የድህነት፣ የባርነትና የሰቆቃ ህይወት በማየት በሚደሰቱ ጸረ ሃገርና ህዝብ ሃይሎች እጅ ወድቃ አበሳዋን ያየችባቸው አመታት ናቸው። ግንቦት 20 የተባለውን የዛሬውን የወያኔዎች በአል የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስበው፣ በሃዘን በቁጭትና በንዴት ነው። የወያኔ እድሜ እንዲረዝም ሳይሆን እንዲያጥር በመመኘት፣ በመጸለይ፣ በመደራጀትና በመታገል ነው። የግንቦት7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ስሜትም ከህዝብ ስሜት የተለያ አይደለም። ለዚህም ነው በወያኔ የፈንጠዝያ እለት ውደቀታቸው የማይቀር መሆኑን የምናረዳቸው።
ውድመት ለዘረኛውና ለዘራፊው ጸረ-ሃገርና ጸረ -ህዝብ ጉጅሌ
እርገት ለኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት የእኩልነት የፍትህና የአንድነት ፍላጎት