የኦሮሞ ፈዴራሊስት ዋና ጸሃፊ ከ40 በላይ አባላቶቻቸው መታሰራቸውን ገለጹ

የወያኔ አገዛዝ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሰሜን አፍሪካው አይነት ህዝባዊ አመጽ ሊነሳብኝ ይችላል  ከሚል ፍርሃት በርካታ ወጣቶችን በሰበብ አስባብ እያሰረ እንደሚገኝ የግንቦት 7 ዘጋቢ ከአዲስ አበባ  በላከልን ሪፖርት ገለጸ።

እንደዘጋቢያችን ሪፖርት አዲስ አበባን ጨምሮ ባሉት ትላልቅ ከተሞች ብዛት ያላቸው የደህነንትና የፈደራል ፖሊስ አባላት ከመመደባቸውም በላይ ወያኔ ባሰማራቸው ፖሊሶችና የደህንነት ሠራተኞች  ካለመተማመን ይመስላል የህወሃት አባላት የሆኑት ታማኝ ወጣቶች ከትግራይ ክልል ተመልምለው  በትላልቅ ከተሞች ውስጥ ተበትኖአል ።

ይህ በዚህ እንዳለ የኦሮሞ ኮንግረስና የኦፌዲን አመራር አባላት በየግል ለኢሳት በሰጡት መረጃ ከ40 በላይ አባላቶቻቸው ባለፉት 3 ቀናት ውስጥ መታሰራቸውንና አንዳንዶቹ ፍርድ ቤት ቀርበው የቱንዚያን አይነት ህዝባዊ አብዮት ለመቀስቀስ ትንቀሳቀሳላችሁ በሚል ክስ መወንጀላቸውን፤  የተቀሩት ግን የት እንዳሰሩዋቸው እንኳን ለማወቅ እንዳልተቻለ ለመረዳት ተችሎአል። እንደሁለቱ የኦሮሞ ድርጅቶች መረጃ በርካታ የኦሮሞ ተወላጆች ተመሳሳይ ማዋከብና እንግልት እየተፈጸመባቸው እንደሆነ ይህም ወያኔ በኦሮሞ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ካለው ተከታታይ የጥቃት  እርምጃ አንዱ እንደሆነ ለማወቅ ተችሎአል። በሰሜን አፍርካ እና መካከለኛው ምስራቅ እየትካሄደ ያለው ህዝባዊ አብዮት መለስ ዜናዊን ምን ያህል እረፍት እንደነሳው የቱንዚያው አይነት አብዮት ይነሳብናል ብዬ ሳስብ አላድርም በማለት ያደረበትን ስጋት ከፍተኛነት በተዘዋዋሪ ገልጾአል ባለፈው ቅዳሜ ጋዜጣዊ መግለጫው።