መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ የአንድ ፓርቲ ስርአት የለም ሲል ተመጻደቀ

የቪኦኤ አዲስ አበባ ዘጋቢ ፒተር ሄንሌይን በኢትዮጵያ የአንድ ፓርቲ ሲስተም ስለመኖሩ ላቀረበለት ጥያቄ፤ ውሸት የማይሰለቸው ዘረኛውና አምባገነኑ መለስ ዜናዊ አይኔን ግምባር ያርገው በሚል የተለመደ ቅጥፈቱ “እንደጃፓንና ቦትስዋና አንድ ጠንካራ ፓርቲ እንጅ የአንድ ፓርቲ ስርአት የለም” በማለት ተመፃድቋል። በጃፓንም ሆነ ቦትስዋና ለረጂም ጊዜ ስልጣን ላይ የቆዩት ፓርቲዎች በሃገራቸው ውስጥ በሰፊው የህዝብ አመኔታን አግኝተው የህዝብ ድምጽ ማጭበርበር ሳያስፈልጋቸው ወይንም በህዝብ የተመረጡትን መግደል፤ ማሰርና ከሃገር ማሰደድ ሳያስፈልጋቸው ስልጣን ላይ የቆዩ ኡሁን እንጂ እንደ መለስ ዜናዊና ቢጤዎቹ ግለሰቦች ለአስርና ላሃያ ዓመታት በስልጣን ላይ የቆዩበት ወቅት አልተመዘገበም ።

ከዚህም ሌላ የመናገር የመሰብሰብ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን መገደብ ሳያስፈልጋቸው የሃሰት የልማት እድገት ቁጥር ሳይፈበርኩ በአለም ዘንድ ዝናን ያተረፈ መሰራታዊ የእድገት ለሃገራቸው ያስመዘገቡ መሆኑን መለስና ቢጤዎቹ ልብ ብለውት አያውቁም ተብሏል። መለስ ዜናዊ አንድም ተቃዋሚ ፓርቲ እንዳያልፍ በካድሬዎቹ አማካኝነት ገድቦ ከያዘ በኋላ 99.6% አግኝቻለሁ በማለት በቀድሞ የኮሚዩኒስት ሃገራት በስልጣን ላይ የነበሩ ባለ አንድ ፓርቲ ስራቶች ሲከተሉ የነበሩትን መንገድ ተግባራዊ አድርጓል። ለማወናበድና ለመቅጠፍ በማስረጃነት የሚጠቅሳቸው እንግሊዝ ቦትስዋና ጃፓን አንድም ወቅት በንደዚህ አይነት ውጤት አሸነፍንበት ያሉበት ወቅት እንደሌለ ይታወቃል።

በቪኦኤ ጋዜጠኛ ወያኔ 99.6% አሸንፊያለሁ ስላለው ምርጫ የታዛቢ ቡድን ሪፖርት ተጠይቆ የሰራው ሴራ የተጋለጠበት መለስ ዜናዊ “የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ግምገማ ሪፖርት ቢዘገይም አያስጨንቀኝም ከዋናውና ማጠቃለያ ሪፖርታቸው በፊት ያቀረቡልኝ የመጀመሪያ ሪፖርት አያስደስትም እናም እንደ መረጃ ለመያዝም የሚየስደፍር አይደለም ብሏል። የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በመጀመሪያ ግምገማ ሪፖርቱ የ2010ሩን ምርጫ ግልጽነት የጎደለው እና ዓለማቀፋዊ መስፈርቶችን የማያሟላ ነው ማለቱ ይታወሳል።