የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎች ዛሬ ፍቼ ማሠልጠኛ ጣቢያ ይገባሉ

– 41.5 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞላቸዋል

በታምሩ ጽጌ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በልመና ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ የጎዳና ላይ ተዳዳሪ ወገኖችን፣ ዛሬ ፍቼ ከተማ ውስጥ ወደሚገኘው ማሠልጠኛ ጣቢያ እንደሚያስገባቸው በአስተዳደሩ የሠራኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ገለጹ፡፡