የፀረ ሙስና ምክትል ኮሚሽነር ከኢሕአዴግ አመራርነት ወደዕጩ አባልነት ዝቅ ተደረጉ

‹‹ካልተሳሳትኩ ግለሰቦች የፈጠሩት የሥልጣን ሽኩቻ ይመስለኛል››

አቶ አዲሱ መንግሥቱ

በታምሩ ጽጌ

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የኢህአዴግ አባላት ሰሞኑን ባደረጉት የአንድ ቀን ግምገማ፣ ምክትል ኮሚሽነር አዲሱ መንግሥቱን ከከፍተኛ አመራርነት ወደዕጩ አባልነት ዝቅ አደረጓቸው፡፡