የመለስ ዜናዊ አስገራሚ ቃለ-ምልልስ ሲዳሰስ!
እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)
ጠ/ሚ/ሩ ቃለምልልስ እየሰጡ ነው… ቅዳሜ መጋቢት 3/2ዐዐ3 …በዚያን ሰሞን ሞላ ብሎ የነበረው ሰውነታቸው አሁን ከሳ ብሏል… ውይ! ውይ! ውይ!… እኔን! ግን… ግን… ከትላንት ወዲያ ቱኒዚያ፣ ትላንት ግብፅ፣ ዛሬ ደግሞ ሊቢያ እየተፈራረቁባቸው ከሳ ማለትማ ይነሳቸው እንዴ?… «ኑሮ ካሉት መቃብርም ይሞቃል» እንጂ፣ የሰሞኑ የመለስ የስጋት ኑሮ «ውስጡን ለቄስ» እንደተባለው ነው… የስቃይ ኑሮ!… አሳዛኝ ኑሮ!… እኔን!