እንደጠላት ለሚታይ ሕዝብ ድጎማ ለምን?

ይነጋል በላቸው

የፕ/ር እንድርያስ እሸቴን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንትነት መሰናበት ልዩ የሚያደርጉ ሁለት ሰሞነኛ ክስተቶች አሉ። ቀዳሚውና ከዚሁ ግለሰብ ጋር በቀጥታ የሚገናኘው የወያኔ መንግሥት ቅሌትን እንደ ክብርና ሞገስ የሚቆጥር መሆኑን የገለጸበት መንገድ ነው። እንድርያስ እሸቴ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ድራሹን ማጥፋቱ በመለስ ዜናዊ አድናቆትና ከፍተኛ ዋጋ ተሰጥቶት ለማን ደስ ይበለው በሚል ይመስላል ሰውዬው በሚኒስትርነት ማእረግ የጠ/ሚንስትሩ የአቶ መለስ ‹አማካሪ› እንዲሆን ተሹሟል።