የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ እንሆ መሪህ

ግርማ ካሣ

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ልትፍታ እንደምትችል ከአንዳንድ ምንጮች አንዳንድ ፍንጮች ያገነሁት ከአንድ ሳምንት በፊት ነበር። እንደዚያም ሆኖ ግን ያለፈው ዓመት አዲስ ዓመት መግቢያ አካባቢ ትፈታለች የሚል ወሬ ተወርቶ ስላልተፈታች፣ በዚህ ዓመትም ሙሉ ለሙሉ ትፈታለች የሚል ተስፋ በልቤ አልነበረም። በእርግጠኝነት እንደምትፈታ ድረ ገጾች ማክሰኞ መስከረም 26 ቀን 2002 ዓ.ም ዘገባ እስኪያወጡ ድረስ፣ በአይምሮዬ ውስጥ ጥያቄው ”መቼ ይሆን ነው የምትፈታው? ” የሚለው ነበር።