ኢትዮ ቴሌኮም ያልተመደቡ ሠራተኞችን ዛሬ ያነጋግራል

– በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች አልተመደቡም

በታምሩ ፅጌ

የኢትዮጵያ ቴሌኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን፣ ኢትዮ ቴሌኮም በሚል ስያሜ እንደ አዲስ ከተዋቀረ በኋላ፣ በአዲሱ አወቃቀር ያልተመደቡ ሠራተኞችን ዛሬ በአምባሳደር ሲኒማ ሰብስቦ ያነጋግራል፡፡