ተቃውሞው ቀጥሏል::የአዲስ አበባ ድሬዳዋ መንገድ የተዘጋ ሲሆን – በባሌ ሮቤ ደግሞ ተማሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ::

#Ethiopia#Oromoprotests : ተቃውሞው ቀጥሏል::የአዲስ አበባ ድሬዳዋ መንገድ የተዘጋ ሲሆን – በባሌ ሮቤ ደግሞ ተማሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ:: #MinilikSalsawi#Hirna#BaleRobe
Minilik Salsawi – ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ የሚወስደው ዋናው መንገድ በሂርና ነዋሪዎች መዘጋቱ ታወቀ::በሂርና ተማሪዎች እና ገበሬዎች ያደረጉትን ተቃውሞ ተከትሎ የወያኔ አግኣዚ ወታደሮች ሕዝቡን ለመግደል ወደ ሂርና ቢገሰግሱም ሕዝቡ ራሱን ለመከላከል ወደ ሂርና የሚያስገቡ የተለያዩ ዋና ዋና እና መጋቢ መንገዶችን በመዝጋት ላይ መሆኑ ታውቋል::በዚህም ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን በማለዳ የተነሱ አውቶብሶች እና ከባድ መኪኖች ሚኒባሶች መንገድ ላይ ለመቆም ተገደዋል::
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና የባሌ ሮቤ ተማሪዎች ተቃውሞ ማሰማታቸው ታውቋል::በዛሬው እለት በባሌ ሮበ ከተማ ተማሪዎች የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን እና የወያኤ አገዛዝ የሚያካሂደው ግድያ በመቃወም አደባባይ ወጥተው ተቃውሞ አሰምተዋል::


