በቀይ ሽብር ሰማዕታት ማኅበሩ በታዩ ብልሹ አሠራሮች ላይ ዛሬ ሪፖርት ይቀርባል

–    ጠቅላላ ጉባዔው ተጠያቂ የሚያደርጋቸው አባላት እንደሚኖሩ ተጠቆመ

በቀይ ሽብር ሰማዕታት ቤተሰቦችና ወዳጆች ማኅበር ውስጥ ደርሰዋል የተባሉ ብልሹ አሠራሮችን እንዲያጣራ ጥቅምት 3 ቀን 2004 ዓ.ም. የተቋቋመውና ችግሮችን ሲያጣራ የከረመው ኮሚቴ ሪፖርቱን ዛሬ ይፋ ያደርጋል፡፡