እናቴ፣መንግስቷ እና መሬቷ

አቤ ቶኪቻው

ወዳጄ እንዴት ሰነበቱልኝእውነቱን ለመናገር በየሳምንቱ ለሀገሬ አንድ ለእናቱ የሆነችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ በየሳምንቱ ብከሰት ደስታዬ ወደር አልነበረውም። ነገር ግን ጋዜጣዋ የምትውለውአርብ አርብ ይሸበራል እየሩሳሌምበተባለበት አርብ ቀን በመሆኑ የኔ ነገር ደግሞ በተለይ ከዚህ ከስደት በኋላ አንዳንዴ የምፅፋቸው ፅሁፎችፆም የነካካቸውእየሆኑብኝ የጦም ሀገር ለሆነችው ኢትዮጵያዬ አልሆን እያለኝ ስተወው፤ ስተወው ቆይቼ በዛሬው አርብ ግን በተቻለኝ አቅም ጦም ያልነካካው ጨዋታ ይዤ አዲሳባ ብቅ ብዬ ነበር።