የሚሰባበረው አጥንት ድምፅ

ስለሴት ህፃናት ወታደሮች የሚያወሳው ይህ ፅሁፈ-ተውኔት ካናዳ ውስጥ ነው የተፃፈው፤ ሱዛኔ ሌቤው በተባለች ፀሀፌ-ተውኔት። ቤልጂየም ውስጥ ለመድረክ ከበቃ በኋላ አሁን በምስራቅ አፍሪቃ ሀገራት ለእይታ በመዞር ላይ ነው። መድረኩ ላይ ሶስት ተዋንያን በአንድ ተዋጊ ቡድን በግዳጅ ለውትድርና የተመለመሉ ህፃናት ሴቶችን መከራ ያሳያሉ።