20 ዓመት ስንት ነው
ግርማ ደገፋ ገዳ
ኢሜይል አስጠላፊ፣ ገዢውን ማኳኳያ ራዲዮ አየር ባለቤት፣ የማወናበጃ መጽሔት አዘጋጅ፣ የተዘረፈ ዶላር አስተላላፊ፣ የፕሮፓጋንዳ ለቅላቂ፣ የሚሰረቅ እቃ ኤክስፖርተር፣ በልማት ስም የዘረፋ አማካሪ፣ የራቁት ዳንስ ቤት ባለቤት፣ የጸጥታ ሰራተኛና ወሬ አመላላሽ ሆነው ኢሕአዴግን ከሚያገለግሉት መሃል፤ አብዛኛዎቹ ሚሊዮነር ናቸው። እነዚህ ሰዎች፣ በሕዝብ ስም ተለምኖ ከሚመጣው ገንዘብ ላይ ድርሻቸውን ለማፈስ ብለው፤ ኮቴያቸው ባሪያ እንዲሆን ፈቅደዋል። በዛሬው ጽሁፌ፣ የዘረፋ ጥቅማቸውን እያስጠበቁ መንግሥትን ስለሚያኳኩሉ፣ ስለዘራፊው መንግሥትና የፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ተወሽቀው ስለሚያሾፉ ዳኞች በጥቂቱ የምለው ይኖረኛል።