የቤይሩት አውሮፕላን አደጋ ተጎጂ ቤተሰቦች ኢንሹራንስ አልተከፈላቸውም
የመታሰቢያ ሐውልት እየተሠራላቸው ነው
በቃለየሱስ በቀለና በብርቱካን ፈንታ
ባለፈው ዓመት በጥር ወር በቤይሩት አቅራቢያ ድንገተኛ አደጋ በደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ሕይወታቸውን ላጡ ተሳፋሪዎችና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ቤተሰቦች እስካሁን ድረስ ኢንሹራንስ እንዳልተከፈላቸው ታወቀ፡፡