የተስፋው ቃል፣ የአህአዴግ ቃል

ተመስገን ደሳለኝ

ተስፋ ቆርጬ አላውቅም። ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር ሳያጋጥመኝ ቀርቶ አይደለም። ብዙ ጊዜ ገጥሞኝ ያውቃል። ነገር ግን የብዙ ሀገራት ተሞክሮን ካየክ ተስፋ እንድትቆርጥ አይገፋፋህም። ለምን? ካልከኝ ብዙዎች ‹‹ሞቱ፣ ተቀበሩ›› ሲባሉ እንደ ገና መግነዛቸውን በጥሰው ሲያቸንፉ ታያለህና። በሀገራችንም ቢሆን ‹‹አለቁ፣ ደቀቁ›› የተባለላቸው ሟርቱን አቸንፈው አይተሀል። ‹‹እፍኝ የማይሞሉ…›› ሲባል የነበረበትንም ዘመን መቼም ትረሳዋለህ ብዬ አላስብም።