ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ወደ አሜሪካ ሄዱ
![]() |
| ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል |
(ደጀ ሰላም፤ ኖቬምበር 13/2010፤ ኀዳር 4/2003 ዓ.ም)፦ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን ሆነው የተመደቡት ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ዛሬ ኅዳር 4/ 2003 ዓ.ም በዲሲና አካባቢው አቆጣጠር ከጠዋቱ 3 ሰዓት (9:00 AM) ዋሽንግተን ዲሲ መግባታቸው ታወቀ:: ዳላስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እና ጥቂት ምእመናን በቦታው በመገኘት አቀባበል ተደርጎላቸዋል:: የብፁዕነታቸው ወደ ዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት መሄድ በሀገረ ስብከቱ እውቅና ይኑረው አይኑረው ለጊዜው ባይታወቅም፤ በአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ ላይ ግን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አልነበሩም::
(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)
