በስዊድን ’’እውነትም እኛ …” ተመረቀ

ግምገማና ውይይት ተደረገ

Sweden, Stockholm 27th November 2010

Ethiopia Zare (ሰኞ ኅዳር 27 ቀን 2003 ዓ.ም. December 6, 2010)፦ በጋዜጠኛና ደራሲ አበራ ለማ ተገጥሞ በራሳቸው አንባቢነትና በአቶ ክብረት መኮንን የምስልና ድምፅ ቅንብር የተደረገለት ”እውነትም እኛ …” የተባለ ሃያ አምስት ግጥሞች የያዘ ዲቪዲ የግጥም መድብል ቅዳሜ ኅዳር 18 (ኖቬምበር 27) ቀን በስቶክሆልም ከተማ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ተመረቀ።