ከ146 ሺሕ ብር በላይ ይዛ ልትወጣ ስትል በተያዘች አሜሪካዊ ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ

(በሚኪያስ ሰብስቤ)

የፌዴራሉ አንደኛ ደረጃ ልደታ ምድብ ችሎት ገደብና ቁጥጥር የተደረገበትን 146,683 የኢትዮጵያ ብር ይዛ ልትወጣ ስትል ተይዛለች በሚል፣ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዓቃቤ ሕግ ክስ ተመስርቶባት ጥፋተኛነቷ በፍርድ ቤቱ የተረጋገጠባት አንዲት አሜሪካዊ በሦስት ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወሰነ፡፡