‹‹ሀገር በእጃችን…›› (ሊያነቡት የሚገባ)

ተመስገን ደሳለኝ

(እለተ እሁድ በ22/04/04 የምሁራኑ ፊት-አውራሪ (የሚያምኑበትን በማንፀባረቅ)፤ እንዲሁም የ‹‹መባል ያለበት መባል አለበት›› ፍልስፍና ተከታይ የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ በመኢአድ ቢሮ ተገኝተው ‹‹ህጋዊ አስተዳደር እና የመብት ጥያቄ›› በሚል ርዕስ ስር አንድ ጽሁፍ አቀረቡ። ፅሁፋቸውንም ሀሳብ ወደ መሬት አውርደው ለአድማጭ በሚገባ መልክ ተነተኑ። በትንታኔአቸውም የአፄ ቴዎድሮስ ታሪክ ፀሐፊ ከነበሩት አለቃ ዘነበ እንዲህ የሚል ቃል መዋሳቸውን ነገሩን። ‹‹…ሀገር በእጃችን…።›› አፄው የዘመነ መሳፍንትን የስልጣን መተራመስ ተሻግረው ማእከላዊ መንግስትን ለመመስረት ሲጣደፉ የስልጣን ጠቅላይነታቸውን ‹‹ሀገር በእጃችን›› ሲሉ ፍካሬያዊ ትርጓሜ ሰጡት። እነሆ አለቃንም ዶ/ሩንም ደርቤ አመስግኜ ቃሉን ለዚህ ፅሁፍ ርእስ ይሆነኝ ዘንድ ተዋስኩ)