የተሻረው የመንግሥት ዕርምጃና የዋጋ ግሽበት ከዓመት በኋላ

መንግሥት ልክ የዛሬ ዓመት፣ ለገና ዋዜማ የዋጋ ቁጥጥር ማድረግ እንደጀመረ አስታውቆ 18 ያህል ሸቀጦች ላይ የመሸጫ ዋጋ ዝርዝር በጋዜጣ እያወጣ፣ በሬዲዮና ቴሌቪዥን እያስነገረ ዋጋ አረጋጋለሁ በማለት የወሰደው ዕርምጃ መንፈቅ ሳይሞላው ለማንሳት መገደዱን ሳይወድ ያስታወቀው አምና ነበር፡፡