የቁም ከብትና የዶሮ ዋጋ ንሯል

የፊታችን ቅዳሜ ተከብሮ የሚውለውን የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ ለገበያ የቀረቡት የቁም ከብቶችና ልዩ ልዩ ዓይነት ዶሮዎች የሽያጭ ዋጋዎች፣ በትርፍ ላይ ብቻ ያተኮሩና የኅብረተሰቡን አቅም ያላገናዘቡ መሆናቸውን ገበያተኞች ገለጹ፡፡