ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የቅዱስ ገብርኤልን በዓል በዲሲ አከበሩ

የመኖሪያቸውና ጽህፈት ቤታቸው ግንባታ እየተጠናቀቀ ነው!

የበአሉ እለት፡ በቤተመቅደስ ውስጥ መለስተኛ ረብሻ ተነስቶ ነበር!

Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓ.ም. January 2, 2011)፦ በውጭ ሀገር በስደት ላይ የሚገኘውና ህጋዊው ሲኖዶስ ብጹዕ ወቅዱስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ አቡነ መርቆሪዮስ መቀመጫቸውን በአሜሪካዋ መናገሻ ዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ እንደሚያደርጉ እና ጽህፈት ቤታቸውና የመኖሪያ ቤታቸው ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ።