አቶ በረከት ምን ነካቸው? ለካስ ጉድ ሳይሰማ የፈረንጆች ገናም አይመጣም!
አቤ ቶኪቻው
የፈረንጆች ገና መጣ። እንንኳን መጣ! የእኛም በቅርቡ ይመጣል። እስከዛው ግን እንኳን ለፈረንጆቹ ገና አደረሰን እንባባል። ያው እንደሚታወቀው አነዚህ ፈረንጆች ገናቸውን ባከበሩ በሳምንቱ አዲስ አመታቸውን ደግሞ ያክብራሉ። ታድያ ይሄኔ እነርሱ አመት ባል ባመትባል ሲደራርቡ እና እረፍት በእረፍት ሲብነሸነሹ ፈረንጅ የያዘው ዶሴ ተሸፈፍኖ መተኛቱ ነውና፤ ከፈረንጅ ጉዳይ ያለው ሰው ቻል ማድረግ ይገባዋል ማለት ነው።