ዲሞክራሲን ያያችሁ? (ክፍል 1)

ሉሉ ከበደ

‘’ንስሀዬ’’ በሚለው ያለፈ ጽሁፌ መለስ ዜናዊ ስልጣኑን ለሽግግር መንግስት እንደሚያስረክብ ቃል ገብቶልናል። ምኞት አይከለከልም፤ የቢሆን ተስፋም ተዘግኖ አያልቅም። ቀጥሎ እንደግዲህ የኛ ተግባር የሚሆነው ከመለስ በሗላ መልሶ እዚያው ጭቃ ውስጥ ይዞን የሚሰጥም ወፈፌ ቡድን መልሰን ስልጣን ላይ እንዳናወጣ፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ነው። እንዴት?.. በሽግግሩ መንግስት በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ራሳቸውን አጠናክረውና አደራጅተው፤ ለምርጫ እንዲወዳደሩ የሚፈቀድላቸው ህብረብሄር ፓርቲዎች መጀመሪያ በራሳቸው ውስጥ ዲሞክራሲያዊ አሰራር አለ ወይ? መደማመጥ መቻቻል አለ ወይ? ብለን መመርመር መጠየቅ ይጠበቅብናል።