የኢህአዴግ መንግሥት አቶ ስዩም መስፍንን ወደ ቻይና ላከ
Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 9 ቀን 2003 ዓ.ም. November 18, 2010)፦ ’መተካካት’ በሚል መርኅ የሥልጣን ለውጥ እንደሚያደርግና በአዳዲስና ወጣት ተሿሚዎች እንደሚተካ ቃል የገባው የኢህአዴግ መንግሥት፤ የቀድሞ ቱባ ቱባ ባለሥልጣናቱን በቋሚ ወይንም በባለሙሉ ሥልጣን አምባሣደርነት መሾሙን ካሳወቀ በኋላ፤ ትናንት አቶ ስዩም መስፍንን ወደ ቤጂንግ እንደሚልክ ይፋ አደረገ።