ኦባንግ ሜቶ ኦታዋ ገባ፡ በኮንጎዎች የተቃውሞ ሰልፍ ላይም ተሳተፈ

“የኦታዋና ቶሮንቶ ኢትዮጵያዊያንን እንቅስቃሴ ያሳድጋል” ተብሎ ተስፋ ተደርጓል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ህዳር 28 ቀን 2004 ዓ.ም. December 8, 2011)፦ የጋራ ንቅናቄ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ በእንግሊዘኛው Solidarity Movement for New Ethiopia የተባለው የተባለው መቀመቻው በሰሜን አሜሪካ የሆነ የኢትዮጵያዊአን የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት መስራችና ስራ አስኪአጅ አቶ ኦባንግ ሜቶ፡ ቀድሞ ይኖርበት ከነበረው ሳስካቱን ከተማ ወደ ካናዳ ዋና ከተማ ኦታዋ በዚህ በያዝነው ሳምንት መዛወሩ ታወቀ።