የፀጥታው ምክር ቤት በተለሳለሰው የኤርትራ ማዕቀብ ላይ ነገ ድምፅ ይሰጣል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የፀጥታው ምክር ቤት ላለፉት በርካታ ወራት ሲወያይበት የቆየውና በጋቦን ተዘጋጅቶ በቀረበው በኤርትራ ላይ በሚጣለው የማዕቀብ የውሳኔ ሐሳብ፣ በነገው ዕለት ድምፅ እንደሚሰጥበት ይጠበቃል፡፡