በብርቱካን ስም መወጋገዝና መለያየት ይቁም!

ግርማ ካሣ ([email protected])

”ከፌዴሬሽኑ ጀርባ ልንሰለፍ ይገባል” በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ጽሁፍ፣ እጅግ በጣም በርካታ ምላሾች በኢሜል ደረሱኝ። ኢሜሎቹ በሙሉ የተቃውሞ ኢሜሎች ናቸው። አንዳንዶቹ ከመቃወም አልፈው ስድብና ዛቻም አዝለዋል።