የኢትዮጵያ ጦር በድጋሚ ወደ ሶማሊያ ሊዘምት ነው
“ፕሬዝዳንቱ አልፈለጉም” የሶማሊያ ባለስልጣን
“ተጠቃሚው አል-ሻባብ ነው” የፖለቲካ ተንታኞች
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 9 ቀን 2004 ዓ.ም. November 19, 2011)፦ የሶማሊያ አብዛኛውን ክልል የተቆጣጠረውና ከአልቃይዳ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አለው የሚባለውን አል-ሻባብን ለመመንጠር፤ የአፍሪካ ህብረት በድምሩ 10 ሺህ የሚገመት ጦር ለመላክ እየሞከረ ሲሆን የኢትዮጵያን ጦር ተሳትፎ በተመለከተ ግን ካሁኑ አወዛጋቢ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው።