የአፍሪካ ኅብረት ሆቴል ፕሮጀክት በድጋሚ ተስተጓጎለ

ሜፖ በተባለው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት እየተገነባ የሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ሆቴል ፕሮጀክት፣ ለአራት ወራት ያህል ግንባታው በመቋረጡ ፕሮጀክቱን በእጅጉ ሊያጓትተው እንደሚችል የውስጥ ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡