የኢትዮ ቴሌኮም ዋነኛ ደንበኞች በአገልግሎት መማረራቸውን ገለጹ

ኢትዮ ቴሌኮም ዋነኛ ከሚላቸው የኮርፖሬት ደንበኞቹ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ በሒልተን ሆቴል ባካሄደው የሐሳብ ልውውጥ መድረክ፣ ዋነኛ ከሚባሉት ደንበኞቹ ያልጠበቀው ጠንከር ያለ ትችትና ቅሬታ እንደተሰነዘረበት ስብሰባውን የታደሙ ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡