በደቡብ ክልል ኦዲተሩን ያስገደሉ ባለሥልጣናትና ገዳዮቹ ከዕድሜ ልክ እስከ 12 ዓመታት ተፈረደባቸው
(በታምሩ ጽጌ)
በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት በቤንች ማጂ ዞን በሺቢንች ወረዳ ሚዛን ከተማ ውስጥ የታክስ ሽያጭ ክፍል ሠራተኛ፣ የዞኑ የሕዝብ አደረጃጀት ኃላፊ፣ የታክስ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊና አንድ ባለሀብት በጋራ በመሆን አላግባብ ያጠፉትን የመንግሥትንና የሕዝብ ገንዘብ ለመንግሥት ሊያጋልጠን ይችላል በማለት፣ የወረዳውን የኦዲት ሠራተኛ በማስገደላቸው ከነገዳዮቹ ጭምር ከዕድሜ ልክ እስከ 12 ዓመታት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው፡፡