በመሬት ጉዳይ የተከሰሱ ከ50 በላይ የኦሮሚያ ባለሥልጣናት ጥፋተኛ ተባሉ

– ዛሬ ቅጣት ይጣልባቸዋል

የመሬት አሰጣጥ ሥርዓት፣ ሕግ፣ ደንብና መመርያ በመተላለፍ በክልሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል በሚል ክስ ተመሥርቶባቸው የነበሩት ከ50 በላይ የሚሆኑ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ባለሥልጣናት በትናንትናው ዕለት ጥፋተኛ ተባሉ፡፡