አወዛጋቢው የላይቤሪያ ምርጫ

አወዛጋቢው የላይቤሪያ ምርጫ ጥላ ባጠላበት ሁኔታ ዛሬ ሲካሄድ ዋለ። ቅድመ ምርጫው ለሀገሪቱ ሴት ፕሬዚዳንት ኤለን ጆንሰን ያደላ ነው በሚል ዋነኛ ተፎካካሪው ዊንስተን ተብማን ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸው ተዘግቧል። ትናንት በዋና ከተማዋ ሞንሮቪያ በተቀሰቀ ግጭት ቢያንስ አራት ሰዎች መገደላቸው ይታወቃል።