አዜብ ያለ መለስ፤ የውጭ ሀገር ኑሮና የኢትዮጵያ ተስፋ
አትክልት አሰፋ (ከቫንኩቨር ካናዳ)
አዜብ ያለ መለስ
አሁን…! አሁን…! ባለፈው ሰሞን ነው። ወ/ሮ አዜብ መስፍን መኪና እያሽከረከሩ የትራፊክ ፖሊስ ያስቆማቸዋል። ስህተት ሰርተሻል በማለት ያስቆማቸው ትራፊክ ጥፋቷን ይገልጽላታል። ወ/ሮዋ ጥፋታቸውን አልሸመጠጡም። አዎ አጥፍቻለሁ አንዱን ግን ስታስቆመኝ ተደናግጨ ነው ስህተት የሰራሁት ይላሉ። የትራፊክ ፖለሱም የቅጣት ትኬቱን ጽፎ በጃቸው አስረክቦ የመንጃ ፈቃዳቸውን ይወስዳል። ይሄ በኢትዮጵያ የትራፊክ አሰራር የተለመደ ነው። እናም መንጃ ፈቃድ የሚወሰደው የትራፊክ መምሪያ ተኪዶ፤ ቅጣት ተከፍሎ ነው።