የጀርመን ዉህደት 21ኛ ዓመት በዓል በቦን

በአዉሮጳዉያኑ 1961ዓ,ም ነሐሴ 13 ማለዳ በርሊኖች ከእንቅልፋቸዉ ሲነሱ ያዩት አስደንጋጭ ህልም እንጂ እዉን አልመሰላቸዉም ነበር። ሌሊቱን ተገንብቶ ምስራቅ ምዕራብ ብሎ ጀርመንን ለዓመታት የከፈለዉ ግንብ ቤተሰብ ከቤተሰብ፤ ወዳጅ ከዘመድ፤ ሥራን ከሠራተኛ ሳይቀር አለያየ።