”በሽብርተኝነት ስም የህዝብ መብቶችን ማፈን ይቁም!” መድረክ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም 13 ቀን 2004 ዓ.ም. September 24, 2011)፦ የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አንዱአለም አራጌ፣ የኦፌዴን ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፣ የኦህኮ የጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ኦልባና ሌሊሳ፣ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ናትናኤል መኮንንና አቶ አሳምነው ብርሀኑ፣ ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታየ፣ ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ፣ ጋዜጠኛ ስለሽ ሐጎስ እንዲሁም አርቲስት ደበበ እሸቱ የአንባገነናዊው ሥርዓት ጅምላ እስራት ሰለባ ከሆኑት ጥቂቶቹ መሆናቸውን መድረክ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው መግለጫ ገለፀ።