”አዲሱ ዓመት ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል” ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ

ዳኛ ብርቱካን አዲሱን ዓመት በስዊድን ከኢትዮጵያውያን ጋር አሳለፉ

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላለፉ

ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ Judge Birtukan Mideksa

 

Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም. September 12, 2011)፦ ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከኢትዮጵያውያን ጋር አዲሱን ዓመት ለመቀበል በተዘጋጀ ልዩ ዝግጅት ላይ በመገኘት በስደት ላይ ለሚገኙና በሀገር ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞታቸውን ገለጹ። ዜጎችን ያስጎነበሰውን የየሀገራቸውን ሥርዓት ለሁልጊዜ እንደቀየሩት ህዝቦች ሁሉ፤ በአዲስ ተስፋ፣ በአዲስ ሃሳብ ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናገሩ።