የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስጋት ውስጥ ወድቀዋል

– አምስት የተዘጉ ተቋማት ተማሪዎች ጉዳይ አሳሳቢ ሆኗል
– ቦርዱ ዛሬ ተወያይቶ አቋም ይወስዳል

የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የብቃት ደረጃ ለመለየት ባደረገው ግምገማ መሠረት የወሰደው ዕርምጃ፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል፡፡