መለስ ሲአይኤ እና ኢትዮጵያ (ክፍል-2)

 ሉሉ ከበደ

ዘመኑ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1990 ላይ ነበር። ለደርግ የአስተዳደርና የፖለቲካ ድህነት ምስጋን ይግባውና ሐገራችን ከገንጣይና አስገንጣይ ሀይሎች ጋር ታደርግ የነበረው ትንንቅ በኛ ሽንፈት ወደማክተሙ ሲቃረብ፤ ዋናው ምክንያት የወያኔና የሻእቢያ ጦር ከኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ጀግናና ሐያል ሆኖ ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ ጦርሰራዊት በገጠመው የአመራርና የአስተዳደር ቀውስ የውጊያ ሞራሉ ሊጠገን በማይችል መልኩ ስለተጎዳና ውግያውን ስለተወው፤ በሩ ሁሉ ለጠላት ክፍት ሆኖ በመገኘቱ ነበር።