በሠዓት ዝቅተኛ የክፍያ መጠን በጀርመን

የመራሂተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ክርስቲያን ዲሞክራቶች ኅብረት ፓርቲ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ፓርቲው በቅርቡ በተካሄደው የጀርመን የምክር ቤት እንደራሴዎች ምርጫ አብላጫውን ድምፅ ቢያገኝም፤ ሀገሪቱን በጥምረት አብሮ ሲመራ የቆየው FDP ለምክር ቤት በቂ ድምፅ ባለማግኘቱ ከሌሎች የተቃውሞ ፓርቲዎች ጋር ለመጣመር ድርድር በማድረግ ላይ ይገኛል።